ጋላሞታይቱ
የየሰርጣሰርጧን
በደል እያሰላች
ሀጥያተ : አምሳሏ የሰለለ : ድምጿን እየሞዣዠረች
ቀና : ብላ : ድንገት
ኢየሱስ : ክርስቶስን
ግርምቷን : ጠየቀች
አይሁድ : ሆነህ : እንዴት ?
እኔ : የማውቀው : አይሁድ ከዚያ : ማዶ : መንደር የተሰነደረ
የጎደፈ : ነፍሴን
የፀለመ : እውኔን
እጅ : እየቀሰረ
ስናድር : አንግቶ
ሰናፍሉን : ታጥቆ
ይጀነን : ነበረ
አይሁድ : ሆነህ : እንዴት ?
ባታውቀው : ነው 'ጂ
የእይታ : ደርዟ
ከአድማስ : ባይሻገር
አጠገቧ : ሆኖ
ውሃ : የሚጠይቃት
የእግዚአብሔር ፡ ቃል : ነበር
ቃል : ማለት : ድልድይ : ነው ፤
በእምነት : ከፍታ
በማስተዋል : ድርሳን
ከአብ : ያስታረቀ
' ቃልነት ' : ትንፋሽ : ነው !
የቆሸሸ : ነፍሴን
በደም : አፀዳድቶ
ህይወት : ያረቀቀ
ቃል : ማለት : እውነት : ነው !
ሰማይ : ዘረጋግቶ
መሬት : አነጣጥፎ
በ ' ሁን ' ያፀደቀ
ብስረተ ሰማያት
ሰመመናም : መንገድ
መንገድ : መዳረሻ
የሚያሰናክላት
ስሟ : ለጎደፈ
በስሙ : እንዲሰይማት
የሕይወት : ውሃ : ሰጣት
.
.
ስሟን : ስሰይማት ፦
በጠራራ : ፀሐይ
እንስራዋን : ትታ
ቀትር : 6 : ሰዓት
ያስበረገጋትን
የሰርክ : ጥሟን : ረስታ
ታውደለድላለች
.
.
ምንድን ነው? ስትባል